Telegram Group & Telegram Channel
ከንቱነትን ለከንቱነት የዳረገች አንዲት ሴት!
***
ሳቋ እንደ መስከረም
ፈለገ ብረሃን ሠራፂ ነበልባል
አሃዱ ነፀብራቅ
ከራስ የሚስታርቅ።

ፈገግታዋ አደይ
ሃምራዊና ቢጫ ንፁህ ሠማያዊ
የዘመን ጎህ ምስራቅ
ከጊዜ ከቦታ ከይዞታ ረቂቅ።

ነፍሷ ዘለሠኛ
ምህረት ለተጠማ ልብ የሚንቆረቆር
ህዋስ የሚነዝር በደም የሚዘመር
የሠላምን ሀሴት በክንፎቹ የሚናኝ
እንስፍስፍ እርግብግብ
ከራዲዮን ርግብ።

ልቦናዋ ቅኔ
ከውበት ማህሌት ሌት ቀን የሚዘረፍ
የንመሃ አራራይ
ከፍጥረት ማአዛ ከርቤ ሆኖ 'ሚፃፍ
ቀዳማይ ዳህራይ ጊዜ ቦታ 'ሚገድፍ
ዘላለም አስጥሎ ዘላለም 'ሚነድፍ።

መንፈሷ ንፁህ ወርቅ
ሀቅን የሚፈትን የተፈተነ እንቁ
እንደ ግዮን ገነት እንዳምላክ ደምግባት
የእውነት ማይ ትጥቁ።

ኩርፊያዋ አርሂቡ
አቦል ቶና ብሎ
ከሃሳብ መከዳ ግርምት ያሠናዳ
ከፀፀት ከርግማን ከክፋት የፀዳ።

ከንቱነትን ለከንቱየት የሠጠችው
አንዲት አንድያ ብሩህ ሴት እሷ
ርግማንን የቀደሠች ህግን በፍቅር የምትሽር
ልቦናችን ነው መቅደሷ።

ይህቺ ሴት መልከ ሙሉ ናት
ይህቺ ሴት መልከ ፅኑ ናት
ይህቺ ሴት መልከ ፀጋ ናት
ይህቺ ሴት ፀሃይ አምሳል ናት
ከወዳጅነት ሠማይ ከአብሮነታችን ምእራፍ
ፋፁም ላታዘቀዝቅ
ስፈነጥቅ ካየንበት
ከብቻዋ ህይወት ምስራቅ
መስከረም ሆና የጠባች
መስከረም ሆና የፀናች
በፈገግታዋ አደይ አብሮነታችንን ገምዳለች።

እሷነቷ ለእልፍ ነፍሶች
እሷነቷ ላእላፍ ልቦች
እሷነቷ ለጊዜ እስረኞች
ቅዱስ የአዛን ጥሪ ነው
ቅዱስ መሆንን በቅፅበት
በአፍታ ቡራኬ የሚወስን።

በነፋሷ ዘለሠኛ
በሀቅ ከፍታ እንጉርጉሮ
በልቦናዋ ተመስጦ
ህልውናችን ተማግሮ
ከቢጫ ሃምራዊ ቀለሟ
ሠማያዊ ገጿ ሁለመናችን ተነክሮ
በመንፈሷ ጠብታ ማይ መንፈሳችን ተፀብሎ
አለን ከንቱ ስትለን ከንቱነታችን ተገሎ።

ወደ ፅድቀቷ መዲና
ወደ ጥራቷ ጎዳና
ወደ ውበቷ ጥሞና
በፍቅር እየሠረግን
ፈለገ ብረሃን ሆንን
ሠራፂ ነበልባል ዘራን
ዘላለምን እየሻርን
ህያው ዘላለም አነፅን
እንደ ጳግሜ ባጭር ጣፈጥን
እንደ መስከረም ገፅታ
ማበብ መፍካትን ናኘን
እውነቷ እውነት አፀና
ከሀቂቃቃ ቆረብን
ከራሳችን ጋር ታረቅን።

ተጳፈ
ለኔዋ ከንቱ መዲና
ነሐሴ 30/2014 ሞጆ



tg-me.com/yehangetem/719
Create:
Last Update:

ከንቱነትን ለከንቱነት የዳረገች አንዲት ሴት!
***
ሳቋ እንደ መስከረም
ፈለገ ብረሃን ሠራፂ ነበልባል
አሃዱ ነፀብራቅ
ከራስ የሚስታርቅ።

ፈገግታዋ አደይ
ሃምራዊና ቢጫ ንፁህ ሠማያዊ
የዘመን ጎህ ምስራቅ
ከጊዜ ከቦታ ከይዞታ ረቂቅ።

ነፍሷ ዘለሠኛ
ምህረት ለተጠማ ልብ የሚንቆረቆር
ህዋስ የሚነዝር በደም የሚዘመር
የሠላምን ሀሴት በክንፎቹ የሚናኝ
እንስፍስፍ እርግብግብ
ከራዲዮን ርግብ።

ልቦናዋ ቅኔ
ከውበት ማህሌት ሌት ቀን የሚዘረፍ
የንመሃ አራራይ
ከፍጥረት ማአዛ ከርቤ ሆኖ 'ሚፃፍ
ቀዳማይ ዳህራይ ጊዜ ቦታ 'ሚገድፍ
ዘላለም አስጥሎ ዘላለም 'ሚነድፍ።

መንፈሷ ንፁህ ወርቅ
ሀቅን የሚፈትን የተፈተነ እንቁ
እንደ ግዮን ገነት እንዳምላክ ደምግባት
የእውነት ማይ ትጥቁ።

ኩርፊያዋ አርሂቡ
አቦል ቶና ብሎ
ከሃሳብ መከዳ ግርምት ያሠናዳ
ከፀፀት ከርግማን ከክፋት የፀዳ።

ከንቱነትን ለከንቱየት የሠጠችው
አንዲት አንድያ ብሩህ ሴት እሷ
ርግማንን የቀደሠች ህግን በፍቅር የምትሽር
ልቦናችን ነው መቅደሷ።

ይህቺ ሴት መልከ ሙሉ ናት
ይህቺ ሴት መልከ ፅኑ ናት
ይህቺ ሴት መልከ ፀጋ ናት
ይህቺ ሴት ፀሃይ አምሳል ናት
ከወዳጅነት ሠማይ ከአብሮነታችን ምእራፍ
ፋፁም ላታዘቀዝቅ
ስፈነጥቅ ካየንበት
ከብቻዋ ህይወት ምስራቅ
መስከረም ሆና የጠባች
መስከረም ሆና የፀናች
በፈገግታዋ አደይ አብሮነታችንን ገምዳለች።

እሷነቷ ለእልፍ ነፍሶች
እሷነቷ ላእላፍ ልቦች
እሷነቷ ለጊዜ እስረኞች
ቅዱስ የአዛን ጥሪ ነው
ቅዱስ መሆንን በቅፅበት
በአፍታ ቡራኬ የሚወስን።

በነፋሷ ዘለሠኛ
በሀቅ ከፍታ እንጉርጉሮ
በልቦናዋ ተመስጦ
ህልውናችን ተማግሮ
ከቢጫ ሃምራዊ ቀለሟ
ሠማያዊ ገጿ ሁለመናችን ተነክሮ
በመንፈሷ ጠብታ ማይ መንፈሳችን ተፀብሎ
አለን ከንቱ ስትለን ከንቱነታችን ተገሎ።

ወደ ፅድቀቷ መዲና
ወደ ጥራቷ ጎዳና
ወደ ውበቷ ጥሞና
በፍቅር እየሠረግን
ፈለገ ብረሃን ሆንን
ሠራፂ ነበልባል ዘራን
ዘላለምን እየሻርን
ህያው ዘላለም አነፅን
እንደ ጳግሜ ባጭር ጣፈጥን
እንደ መስከረም ገፅታ
ማበብ መፍካትን ናኘን
እውነቷ እውነት አፀና
ከሀቂቃቃ ቆረብን
ከራሳችን ጋር ታረቅን።

ተጳፈ
ለኔዋ ከንቱ መዲና
ነሐሴ 30/2014 ሞጆ

BY እንደ.....ገጣሚ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 280

Share with your friend now:
tg-me.com/yehangetem/719

View MORE
Open in Telegram


እንደ ገጣሚ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

The lead from Wall Street offers little clarity as the major averages opened lower on Friday and then bounced back and forth across the unchanged line, finally finishing mixed and little changed.The Dow added 33.18 points or 0.10 percent to finish at 34,798.00, while the NASDAQ eased 4.54 points or 0.03 percent to close at 15,047.70 and the S&P 500 rose 6.50 points or 0.15 percent to end at 4,455.48. For the week, the Dow rose 0.6 percent, the NASDAQ added 0.1 percent and the S&P gained 0.5 percent.The lackluster performance on Wall Street came on uncertainty about the outlook for the markets following recent volatility.

Telegram has exploded as a hub for cybercriminals looking to buy, sell and share stolen data and hacking tools, new research shows, as the messaging app emerges as an alternative to the dark web.An investigation by cyber intelligence group Cyberint, together with the Financial Times, found a ballooning network of hackers sharing data leaks on the popular messaging platform, sometimes in channels with tens of thousands of subscribers, lured by its ease of use and light-touch moderation.እንደ ገጣሚ from tw


Telegram እንደ.....ገጣሚ
FROM USA